የኢትዮጵያ ውርስና ቅርስ ማሕበር በሰሜን አሜሪካ ታዋቂው ከያኔ ቴዲ አፍሮ በቅርቡ በለቀቀው የሙዚቃ
አልበም ምክንያት ከመንግሥት አካላት የንብረት ዘረፋ፣ ማስፈራራትና፣ ጫና እየደረሰበት እንደሆነ
የሚያሳዩ የተለያዩ የሚዲያ ዘገባዎችን በጥልቀት እየተከታተለ ነው። ማሕበሩ ይህ ሁኔታ እጅግ
እንዳሳሰበው እየገለጸ ሙዚቃና ስነ-ጥበብ የህዝብ ድምፅ ናቸውና ከያኔዎች ሀሳባቸውን በነፃነት የማቅረብ
መብታቸው እንዲከበርላቸው ይጠይቃል።
