EHSNA-transformed-removebg

የኢትዮጵያ ውርስና ቅርስ ማሕበር በከያኔ ቴዲ አፍሮ ላይ እየደረሰ ባለው ጫና ላይ የሰጠው መግለጫ

የኢትዮጵያ ውርስና ቅርስ ማሕበር በሰሜን አሜሪካ ታዋቂው ከያኔ ቴዲ አፍሮ በቅርቡ በለቀቀው የሙዚቃ
አልበም ምክንያት ከመንግሥት አካላት የንብረት ዘረፋ፣ ማስፈራራትና፣ ጫና እየደረሰበት እንደሆነ
የሚያሳዩ የተለያዩ የሚዲያ ዘገባዎችን በጥልቀት እየተከታተለ ነው። ማሕበሩ ይህ ሁኔታ እጅግ
እንዳሳሰበው እየገለጸ ሙዚቃና ስነ-ጥበብ የህዝብ ድምፅ ናቸውና ከያኔዎች ሀሳባቸውን በነፃነት የማቅረብ
መብታቸው እንዲከበርላቸው ይጠይቃል።