በአል ነጃሲ መስጊድ ላይ ስለደረሰው ጥቃት የተሰጠ መግለጫ
የኢትዮጵያ ውርስና ቅርስ ማኅበር በሰሜን አሜሪካ (ኢ.ው.ቅ.ማ.ሰ.አ.) ጥር 2003 ዓ.ም. ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ የቀደሙ አባቶቻችንና እናቶቻችን ያወረሱንን ታሪክ፣ ትውፊትና ቅርስ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍና ተተኪው ትውልድ በአገራችን ባሕልና ወግ እንዲታነጽ በማድረግ በኩል ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል። ኢትዮጵያ ሉዓላዊነቷና አንድነቷ የተጠበቀ አንዲሁም ዜጎቿ በሰላም የሚኖሩባት አገር እንድትሆን የኢ.ው.ቅ.ማ.ሰ.አ. ጽኑ ምኞት አለው።